Our website uses necessary cookies to enable basic functions and optional cookies to help us to enhance your user experience. Learn more about our cookie policy by clicking "Learn More".
Accept All Only Necessary Cookies

Mengenai Gibre Himamat

የግብረ ሕማማት መጽሐፈ, መጽሐፈ ጾመ ድጓ እና የአጽዋማት ምንባባት

ይህ አፕሊኬሽን ሃምሳ ብር ያስከፍላል።

Gibre Himamat adalah buku Tewahedo Ortodoks Ethiopia yang dibaca pada minggu Suci, minggu terakhir Prapaskah. Buku ini mengandungi bacaan Palm Sunday, Monday Monday, Holy Tuesday, Holy Wednesday (Spy Wednesday), Maundy Thursday (Holy Thursday), Good Friday (Holy Friday), Holy Saturday dan Easter. Buku ini mengandungi bacaan dari Kitab Suci, buku-buku Canonical Ortodoks, Synaxarium, Mukjizat Yesus Kristus, Keajaiban Saint Mary, Ramalan, Buku Doa, Haymanote Abew, Doa Perjanjian, Gedles dan banyak lagi buku gereja Tewahedo Orthodoks Ethiopia.

Tujuan rahsia buku ini adalah untuk mengingatkan kita bahawa Tuhan telah memberi kita keperitan, kematian, kebebasan dan kemuliaan kekal dalam kebangkitan-Nya, dan bahawa Dia adalah Tuhan kehidupan tanpa kesakitan dan kematian, dibaca dan dilatih setiap hari di minggu suci ini

Oleh itu, pola umum doa dan pelayanan Gibre Himamat terdapat dalam buku ini, dan adalah harapan kami yang tulus agar para imam dan jemaat dapat memegang buku ini dan mengikutinya.

መጽሐፈ ግብረ ሕማማት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጌታችንነ የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መከራ መስቀል የሚዘከርበትና በሰሙነ ሕማማት የሚነበብ ታላቅ መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ፣ ከሥርዓት መጻሕፍት ፣ ከትንቢት ፣ ከድርሳናት ፣ ከተአምራት ፣ ከመዝሙራት ፣ ከተግሣጻት ፣ ከሃይማኖተ አበው ፣ ከኪዳን መጽሐፍ ፣ ከመጽሐፈ ስንክሳርና ከአበው መጻሕፍት የተውጣጡ ትምህርቶችንና የጸሎት ክፍሎችን ከሆሣዕና ዋዜማ እስከ ትንሣኤ ባሉት ስምንት ቀናንት በሰዓታት ተከፋፍሎ የተዘጋጀ መጽሐፍ ነው።።

የመሠረቱና ታሪካዊ አመጣጡም ከአባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት ተያይዞ የመጣ ነው። ይኸውም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለሐዋርያት እየተገለጸ እስከ አርባ ቀን ድረስ መጽሐፈ ኪዳንንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተምራቸው ቈይቶ። በአርባ ቀኑም ሐዋርያትን በአንብሮተ እድ ሹሟቸውና ባርኳቸው አርጓል። (ማር ፲፮ ፲ህ። ሉቃ ፳፬ ፤ ፶፩። የሐዋ ሥራ ፩-፱)

ከዚህም በኋላ ሐዋርያት በኢየሩሳሌም ካሉ ምዕመናን ጋር ጾም መጾምንና ትንሣኤውን ማክበር ጀመሩ። በዚህ ጊዜ በጽርሐ ጽዮን ተሰብስበው በደነገጉት የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ፥ ስለ ሰሙነ ሕማማት «ወአንትሙሰ ተዐቅቡ ወግበሩ ተዝካረ ሕማማቲሁእናንተ ግን ጠብቃችሁ የመከራ መስቀሉ መታሰቢያ የሆነውን ሕማማቱን አድርጉ አክብሩ» ሲሉ አዝዘዋል። (ትእዛዝ ፴፩)

ሆኖም ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል ይፋጠኑ ነበረና እንደ ዛሬው ሁሉ ጊዜውን አልወሰኑትም ነበር። ከሐዋርያት ቀጥለው የተነሱ ሊቃውንትም ቢሆኑ እንደዚሁ በዐተ ጾምን ከጥር ፲፩ ቀን እስከ የካቲት ፳፩ ቀን ከጾመ። በኋላ ሰሙነ ሕማማትን ደግሞ ከዐቢይ ጾም ለይተው ከመጋቢት ፳፪ እስከ መጋቢት ፳፰ ቀን በመጾም መጋቢት ፳፱ ቀን ትንሣኤውን ያከብሩ ነበር። ይህ ሥርዓት ሲያያዝ እስከ ድሜጥሮስ ዘመን ደረሰ።

ከ፩፻፹፰ እስከ ፪፻፴ ዓ.ም የነበረው ሊቀ ጳጳስ ድሜጥሮስ በአዘጋጀው የጊዜ መቁጠሪያ (ባሕረ ሐሣብ) ሰሙነ ሕማማት ከዐቢይ ጾም ቀጥታ እንዲሆን ተወስኖአል። ቤተ ክርስቲያንም በቀመረ ድሜጥሮስ ዓመታትን በንዑስ ፤ በማዕከላዊና በዐቢይ ቀመር እየቀመረች አጽዋማት የሚገቡበትንና በዓላት የሚውሉበትን ጊዜ ለምዕመናን ታሳውቃለች።

ስለሆነም የሰሙነ ሕማማት ሥርዓተ ጸሎትና አገልግሎት ሁኔታ ከቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓተ አምልኮት ጋር የተያያዘ ቢሆንም አሁን ያለውን ሥርዓት የያዘ ግብረ ሕማማት ፤ የተሰኘው መጽሐፍ ተዘጋጅቶ በሥራ ላይ የዋለው ከጌታ ልደት በኋላ በ፲፬ኛው ምዕት ዓመት ነው።

ከ፩ሺ፫፻፵ እስከ ፩ሺ፫፻፹ ዓ.ም የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሰላማ ብርሃነ ዐዜብ ከዐረብኛ ወደ ግእዝ እንደተረጎሙት ቀደም ሲል በግእዝ ብቻ ታትሞ በነበረው የግብረ ሕማማት መጽሐፍ ውስጥ ተገልጦአል።

የመጽሐፉ ስያሜም ከጥንተ ስሙ ጀምሮ ግብረ ሕማማት እንደሚባል በመጽሓፉ ውስጥ በብዙ ክፍል ተጠቅሶ ይገኛል። ለዚሁም በቂ የሆነ ምሥጢራዊ ምክንያት እንዳለው ይታመናል።

ምሥጢራዊ ዓላማውም ጌታ በሕማሙ ሕማማችንን ፤ በሞቱ ሞታችንን ፤ በትንሣኤው ዘለዓማዊ ነፃነትንና ክብርን ያጐናጸፈን መሆኑን ከማስገንዘቡም በላይ በባሕርዩ መከራና ሞት የሌለበት ሕያወ ባሕርይ አምላክ መሆኑ በሰሙነ ሕማማት በየአንዳንዱ ቀን ይነበባል ይተረካልም።

በዚህ መሠረት የሰሙነ ሕማማት ጸሎትና አገልግሎት ጠቅላላ ሥርዓት በዚህ መጽሓፈ ግብረ ሕማማት በየክፍሉ ተጽፎ ስለሚገኝ ካህናትም ምዕመናንም መጽሐፉን በመያዝ ሥርዓቱን ለመከታተል ያመቻል የሚል ጽኑእ ተስፋ አለን።

Terjemahan Memuatkan...

Maklumat APLIKASI tambahan

Versi Terbaru

Minta Gibre Himamat Kemas kini 4.0

Dimuat naik oleh

عمر سامي محمد

Memerlukan Android

Android 4.1+

Tunjukkan Lagi

Apa yang baru dalam versi terkini 4.0

Last updated on Nov 9, 2020

Support for target Android 10 (API level 29) included.

Tunjukkan Lagi

Gibre Himamat Tangkapan skrin

Memuatkan Komen...

Juga tersedia untuk platform lain

Bahasa
Langgan APKPure
Jadilah yang pertama untuk mendapatkan akses kepada pelepasan awal, berita, dan panduan permainan dan aplikasi Android terbaik.
Tidak, Terima kasih
Daftar
Berjaya berjaya!
Anda kini melanggan APKPure.
Langgan APKPure
Jadilah yang pertama untuk mendapatkan akses kepada pelepasan awal, berita, dan panduan permainan dan aplikasi Android terbaik.
Tidak, Terima kasih
Daftar
Kejayaan!
Anda kini melanggan surat berita kami.